በማረሚያ ቤት አለመኖራቸው በተገለጸው አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የቀረበው ይግባኝ ውድቅ ተደረገ
በሽብር ድርጊት ወንጀል ተጠርጥረው ክስ ተመሥርቶባቸው ማረሚያ ቤት በሚገኙት በእነ ዘመኑ ካሴ የክስ መዝገብ በመከላከያ ምስክርነት በተቆጠሩት የግንቦት ሰባት አመራር የነበሩት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ በመከላከያ ምስክርነት እንዳይቀርቡ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ቀርቦ የነበረው ይግባኝ ኅዳር 23 ቀን 2008 ዓ.ም....
View Articleፓርላማው ረቂቅ ሕጐችን ከማፅደቁ በፊት በድረ ገጹ ለሕዝብ እንዲደርሱ ሊያደርግ ነው
-ደንቦችንና መመርያዎችን በሦስት ወራት ውስጥ ማውጣት አስገዳጅ ሊሆን ነው አዋጆች ከመፅደቃቸው በፊት በኅብረተሰቡና በባለድርሻ አካሎች ተሳትፎ እንዲዳብሩ፣ ረቂቅ ሕጐችን እንደ አዲስ እየተሠራ ባለው የፓርላማው ድረ ገጽ ላይ እንዲጫኑ ሊደረግ ነው፡፡ ከፓርላማው ጽሕፈት ቤት ሪፖርተር ያገኛቸው መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣...
View Articleየአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅና የግዢ ዳይሬክተር ታሰሩ
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅና የግዢና ንብረት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር በአሥር ሚሊዮን ብር ሙስና ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ታወቀ፡፡ ዋና ሥራ አስኪያጁ አቶ ኤፍሬም ደሳለኝና የግዥና ንብረት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ንጉሤ ታደሰ በቁጥጥር ሥር የዋሉት፣ ኅዳር 21 ቀን 2008...
View Articleበኦሮሚያ የተከሰተው ተቋውሞ የሦስት ሰዎችን ሕይወት ቀጠፈ
-በጎንደር ማረሚያ ቤት ቃጠሎም የ17 ሰዎች ሕይወት ጠፍቷል የአዲስ አበባና የኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ ማስተር ፕላን ላይ በተነሳው ተቃውሞ፣ በኦሮሚያ ክልል ያሉ ዩኒቨርሲቲዎችና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች ከፀጥታ ኃይሎች ጋር በመጋጨታቸው የሦስት ሰዎች ሕይወት ጠፍቷል፡፡ መንግሥት የሟቾች ቁጥር ሦስት...
View Articleየኢትዮጵያ የግብፅና የሱዳን የሚኒስትሮች ቡድን ሱዳን ይገናኛል
-የህዳሴው ግድብ ግንባታ እንዲዘገይ ግብፅ ጥያቄ እያቀረበች ነው የኢትዮጵያ፣ የግብፅና የሱዳን የጋራ ቴክኒክ ኮሚቴ የታላቁን ህዳሴ ግድብ የሚያጠኑ ሁለት ኩባንያዎች ለማግባባት የወሰዱትን ጊዜ ለማሳጠር፣ የሦስቱ አገሮች ስድስት ሚኒስትሮች በሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም ከተማ ከኅዳር 26 ቀን 2008 ዓ.ም. ጀምሮ ለሁለት...
View Articleሳዑዲ ስታር ዝናብ ላይ ጥገኛ ሆኗል
የሼክ መሐመድ አል አሙዲ ኩባንያ ሳዑዲ ስታር የግብርና ልማት ድርጅት በደርግ መንግሥት ዘመን የተገነባውን አልዌሮ ግድብ ከመንግሥት ቢረከብም፣ በመስኖ ማልማት የቻለው 350 ሔክታር መሬት ብቻ ነው፡፡ የተቀረውን ስድስት ሺሕ ሔክታር መሬት በዝናብ ለማልማት የተሞከረ መሆኑ ታውቋል፡፡ ድርጅቱ ግን ከመንግሥት የተረከበው...
View Articleበሙስና የተጠረጠሩት የኦሮሚያ ባለሥልጣን የተመሠረቱባቸው ክሶች ውድቅ ተደርገው እንዲፈቱ ጠየቁ
የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት አባልና የክልሉ ገቢዎችና ጉምሩክ ቢሮ ኃላፊ የነበሩት አቶ ወንድሙ ቢራቱ፣ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጉዳያቸውን የማየት ሥልጣን ስለሌለው የተመሠረቱባቸው ክሶችን ውድቅ በማድረግ ከእስር እንዲፈታቸው ጠየቁ፡፡ ተጠርጣሪው ጥያቄውን ያቀረቡት የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን...
View Articleየሲሚንቶ ገበያ ተቀዛቀዘ
-የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ለሲሚንቶ ፋብሪካዎች ፈተና መሆኑ ተነገረ በኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ እየተፈተነ የሚገኘው የሲሚንቶ ኢንዱስትሪ የገበያ መቀዛቀዝ አሳየ፡፡ አገር ውስጥ የሚገኙ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ዓመታዊ የማምረት አቅማቸው 13 ሚሊዮን ኩንታል ቢሆንም፣ ሽያጩ ግን ከሰባት ሚሊዮን ኩንታል ያልበለጠ መሆኑ...
View Articleየኤቲኤም ማሽን ደንበኞችን ቢያስደንግጥም ንግድ ባንክ ሥጋት አይግባችሁ እያለ ነው
ሰሞኑን በአዲስ አበባ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደንበኞች በኤቲኤም ማሽን ገንዘብ ማውጣት ባለመቻላቸው፣ በአጭር የመልዕክት ጽሑፍ ገንዘብ ማውጣታቸውን በሚገልጸው መልዕክት ከፍተኛ መደናገጥ እየተፈጠረባቸው ነው፡፡ ባንኩ በበኩሉ በጊዜያዊ ገንዘብ ዝውውር የኔትወርክ ችግር ያጋጠመ ቢሆንም፣ የገንዘብ ኪሳራ እንደማይገጥማቸው...
View Articleየኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ውስጥ ወንጀል በመፈጸም የተጠረጠረው ሱዳናዊ ተከሰሰ
ከቻድ ዋና ከተማ እንጃሚና ወደ አዲስ አበባ መንገደኞችን አሳፍሮ ይበር በነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ውስጥ፣ ተጓዦችን በመደብደብ ወንጀል የተጠረጠረው የሱዳን ዜጋ ክስ ተመሠረተበት፡፡ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ አራተኛ ወንጀል ችሎት ክስ የተመሠረተበት ሱዳናዊው አህመድ አልሼክ እድሪስ...
View Articleየሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በአዲስ አበባና በኦሮሚያ ልዩ ዞን ማስተር ፕላን ላይ ተቃውሞ አሰሙ
‹‹አረጋግተን እንዴት ትምህርት መጀመር እንዳለባቸው እየተነጋገርን ነው›› የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የአዲስ አበባና ኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ ማስተር ፕላንን በመቃወም፣ ኅዳር 20 ቀን 2008 ዓ.ም. ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ውስጥ ሠልፍ ወጡ፡፡...
View Articleለቦሌ ኤርፖርት ማስፋፊያ ተጨማሪ 120 ሚሊዮን ዶላር ብድር አስፈልጓል
የአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት የማስፋፊያ ፕሮጀክትን በ225 ሚሊዮን ዶላር በማካሄድ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤርፖርቶች ድርጅት፣ በግንባታው ላይ ተጨማሪ ሥራዎች በመካተታቸው የፕሮጀክቱ ወጪ ወደ 345 ሚሊዮን ዶላር ማሻቀቡን አስታወቀ፡፡ የአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት የመንገደኞች ተርሚናል...
View Articleየኃይል ማመንጫዎች ብልሽት በመላ አገሪቱ የኃይል አቅርቦት እያስተጓጎለ ነው
በጣና በለስና በጊቤ አንድ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች በደረሰ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያና የኤሌክትሮኒክ መቆጣጠሪያ ብልሽት፣ በመላ አገሪቱ የኃይል አቅርቦ ተስተጓጉሏል፡፡ ቅዳሜ ኅዳር 18 ቀን 2008 ዓ.ም. በአገሪቱ ትልቁና 460 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት ላይ በሚገኘው ጣና በለስ የኃይል ማመንጫ...
View Articleሳሊኒ በ1.5 ቢሊዮን ዶላር ጊቤ አራትን ለመገንባት ድርድር ጀመረ
የግንባታ ውል ሳይፈርም በጊቤ አራት ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የሲቪል ምህንድስና ሥራ የጀመረው የጣሊያኑ ግዙፍ ኩባንያ ሳሊኒ ኮንስትራክሽን፣ በመጨረሻ ግልገል ጊቤ አራትን በ1.5 ቢሊዮን ዶላር ለመገንባት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር ድርድር ጀመረ፡፡ ሳሊኒ ኮንስትራክሽን ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ ከአውሮፓ የገንዘብ...
View Articleለቦሌ ኤርፖርት ማስፋፊያ ተጨማሪ 120 ሚሊዮን ዶላር ብድር አስፈልጓል
የአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት የማስፋፊያ ፕሮጀክትን በ225 ሚሊዮን ዶላር በማካሄድ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤርፖርቶች ድርጅት፣ በግንባታው ላይ ተጨማሪ ሥራዎች በመካተታቸው የፕሮጀክቱ ወጪ ወደ 345 ሚሊዮን ዶላር ማሻቀቡን አስታወቀ፡፡ የአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት የመንገደኞች ተርሚናል...
View Articleየመከላከያና የብሔራዊ ደኅንነት ኮሚቴ አባላትን ፓርላማው በተአቅቦ ድምፅ አፀደቀ
የመከላከያና ብሔራዊ ደኅንነት ጉዳዮች ልዩ ኮሚቴ አባላትን ፓርላማው በአንድ የድምፅ ተአቅቦ ሰየመ፡፡ በጥቅምት ወር 2008 ዓ.ም. የፀደቀው የፓርላማው የአሠራርና የአባላት ሥነ ምግባር ደንብ፣ በደኅንነትና በመከላከያ ተቋማት ላይ የሚካሄደውን ክትትልና ቁጥጥር በበለጠ ውጤታማ ለማድረግ የመከላከያና ብሔራዊ ደኅንነት...
View Articleብሔራዊ ባንክ የንግድ ባንኮችን የግዴታ መጠባበቂያ ገንዘብ ከፍ ሊያደርግ ነው
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በባንኮች ላይ የሚጣለውን የግዴታ መጠባበቂያ ገንዘብ ምጣኔ፣ በቀጣዮቹ ዓመታት ወደ 30 በመቶ እንደሚያሳድግ ምንጮች ገለጹ፡፡ የሪፖርተር ምንጮች እንደሚገልጹት፣ በአሁኑ ወቅት ሁሉም ንግድ ባንኮች የኢትዮጵያ ልማት ባንክን ጨምሮ ሁለት ዓይነት የመጠባበቂያ ገንዘብ በብሔራዊ ባንክ በሚከፍቷቸው ዝግ...
View Articleአመፅ በማስነሳት ልዩ ዞን ለማቋቋም ተንቀሳቅሰዋል የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተከሰሱ
ትጥቅ በመያዝ የእርስ በርስ ጦርነት በማነሳሳት የሸኮ ተወላጆችን ከሸኪቾ ብሔሮች በመለየት ‹‹ሸኮ መዠንገር›› የሚባል ልዩ ዞን ለማቋቋም ተንቀሳቅሰዋል የተባሉ አራት ተጠርጣሪዎች፣ ኅዳር 20 ቀን 2008 ዓ.ም. በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ክስ ተመሠረተባቸው፡፡ ተከሳሾቹ በደቡብ ክልል ሸካ ዞን...
View Articleየኅብረት ሥራ ማኅበራት ከገቢ ግብር ነፃ እንዲሆኑና መሬት በምደባ እንዲያገኙ የሚያደርግ አዋጅ ቀረበ
በሥራ ላይ ያለውን የኅብረት ሥራ ማኅበራት አዋጅ በማሻሻል በድጋሚ የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ ማክሰኞ ኅዳር 21 ቀን 2008 ዓ.ም. ለፓርላማ ቀረበ፡፡ ረቂቁ ማኅበራቱ ከገቢ ግብር ነፃ እንዲሆኑና መሬት በምደባ በመንግሥት እንዲያገኙ ይፈቅዳል፡፡ በሥራ ላይ ያለውን የኅብረት ሥራ ማኅበራት አዋጅ ቁጥር 147/1996...
View Articleመምህር ግርማ ወንድሙ በተጠረጠሩበት የነፍስ ግድያ ወንጀል 14 ቀናት ተጠየቀባቸው
በተጠረጠሩባቸው ሁለት የተለያዩ ወንጀሎች ዋስትና ከተፈቀደላቸው በኋላ በነፍስ ግድያ ተጠርጥረው በእስር ላይ በሚገኙት መምህር ግርማ ወንድሙ ላይ፣ ፖሊስ ኅዳር 20 ቀን 2008 ዓ.ም. የጠየቀው የ14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቀደለት፡፡ በፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ፖሊስ...
View Article