ብሔራዊ ባንክ ለፋይናንስ ኪራይ ሥራ ፈቃድ እንዲሰጥ ተፈቀደለት
-የአገር ውስጥ ድርጅቶችን የማሽነሪ ችግር ይቀርፋል -ብሔራዊ ቁጠባን በከፍተኛ ደረጃ ይጨምራል በ1990 ዓ.ም. የፀደቀውን የካፒታል ዕቃ ኪራይ ሥራ አዋጅ በማሻሻል ለካፒታል ዕቃዎች የገንዘብ ኪራይ (ፋይናንስ ሊዝ) እና የዱቤ ግዥ ሥራ በኢትዮጵያ እንዲጀመር ተወሰነ፡፡ ለተጠቀሰው የሥራ ዓይነት ብሔራዊ ባንክ የንግድ...
View Articleአንድነት ፓርቲ በጎንደር የጠራው ሰላማዊ ሠልፍ ለሐምሌ 7 ተላለፈ
- ዘጠኝ አስተባባሪዎች ታስረውብኛል አለ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ የሦስት ወራት ሕዝባዊ ንቅናቄ የትግል ስልት በመንደፍ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ በጎንደር ከተማ ሰኔ 30 ቀን 2005 ዓ.ም. የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ለሐምሌ 7 ቀን 2005 ዓ.ም. መተላለፉን አስታወቀ፡፡ እስካሁን ከ80 ሺሕ በላይ በራሪ ወረቀቶችን...
View Articleለብሔራዊ ስታዲየም ግንባታ ማስጀመሪያ 200 ሚሊዮን ብር በጀት ተፈቀደ
በአገሪቱ እየታየ ባለው የእግር ኳስ ዕድገት ምክንያት በመንግሥት ለተያዘው ግዙፍ የብሔራዊ ስታዲየም ግንባታ በ2006 ዓ.ም. እንዲጀመር ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ሲመደብ፣ ለ2006 ዓ.ም. ብቻ 200 ሚሊዮን ብር ተፈቅዷል፡፡ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትሩ አቶ ሱፊያን አህመድ የአገሪቱን የቀጣይ ዓመት በጀት...
View Articleተሰናባቹ የአዲስ አበባ ምክር ቤት ለሚቀጥለው በጀት ዓመት ከ20 ቢሊዮን ብር በላይ አፀደቀ
ቅዳሜ የተሰናበተው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ለ2006 ዓ.ም. የበጀት ዓመት 20.041 ቢሊዮን ብር በጀት አፀደቀ፡፡ ከዚህ በጀት ውስጥ 12.13 ቢሊዮን ብር ለካፒታል ፕሮጀክቶች፣ 6.8 ቢሊዮን ብር ለመደበኛ ወጪዎች፣ 1.02 ብር ቢሊዮን ለመጠባበቂያ ተመድቧል፡፡ ከካፒታል ፕሮጀክቶች ከፍተኛ በጀት...
View Articleኢንቨስተሮች በኢትዮጵያ ልማት ባንክ ተማረሩ
- ልማት ባንክ ቅሬታቸውን አልተቀበለም ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ከአዲስ አበባ 275 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ሐዋሳ ከተማ የተሰበሰቡ ኢንቨስተሮች፣ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለአገር ውስጥ ኢንቨስተሮች ብድር እየሰጠ አይደለም ሲሉ አማረሩ፡፡ ሐሙስ ሰኔ 27 ቀን 2005 ዓ.ም. የትምህርት ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት...
View Articleበአሥር ዓመት ውስጥ የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር ከስምንት ሚሊዮን በላይ እንደሚጨምር ይጠበቃል
- ከመቶ ሺሕ በላይ ሰዎች ክልል አልባ ሆነዋል በመላ ኢትዮጵያ የሕዝብ ቆጠራ ከተካሄደ ከስድስት ዓመት በኋላ ይፈ የተደረገው አዲሱ የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ ትንበያ፣ በሚቀጥሉት አሥር ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር 94.4 ሚሊዮን እንደሚደርስ በመገመቱ፣ የ8.5 ሚሊዮን ተጨማሪ ሕዝብ ቁጥር እንደሚመዘገብ...
View Articleግብረሰዶም ፈጽመዋል በተባሉ ተጠርጣሪዎች ላይ ምስክሮች ተሰሙ
በሁለት ሕፃናት ተማሪዎቻቸው ላይ የግብረሰዶም ጥቃት ፈጽመዋል በተባሉ ስድስት መምህራን ላይ የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ስድስት ምስክሮች፣ ሰኔ 28 ቀን 2005 ዓ.ም. በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሰባተኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው የምስክርነት ቃላቸውን ሰጡ፡፡ በቦሌ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ሩዋንዳ ተብሎ...
View Articleከንቲባ ኩማ የከተማውን ቁልፍ ማክሰኞ ያስረክባሉ
የከንቲባ ኩማ ደመቅሳ ካቢኔ ለአዲሱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ የከተማውን ቁልፍ ለማስከረከብ ለማክሰኞ ሐምሌ 2 ቀን 2005 ቀጠሮ ይዟል፡፡ በአቶ ድሪባ ኩማ ይመራል ተብሎ የሚጠበቀው አዲሱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በዕለቱ መሥራች ጉባዔውን በማካሄድ የአፈ ጉባዔና የከንቲባ ምርጫ ያካሂዳል፡፡...
View Articleአዲሱ ሹመትና ሽግሽግ
ባለፈው ሐሙስ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የከፍተኛ መንግሥት ባለሥልጣናትን ሹመት በፓርላማ አፀድቀዋል፡፡ የአሥሩ አዲስ ተሿሚዎች ሹመት የፀደቀው በአንድ ድምፅ ተአቅቦና በአብላጫ ድምፅ ነው፡፡ ተሿሚዎቹ በጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ተገኔ ጌታነህ አማካይነት ቃለ መሃላ ፈጽመዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ...
View Articleሃምሳ ኢንዱስትሪዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ባለማግኘታቸው ሥራ ሊጀምሩ አልቻሉም
በኢንዱስትሪ ከተማነቷ በምትታወቀውና የአዲስ አበባ ተጎራባች በሆነችው ገላን ከተማ ውስጥ 50 ኢንዱስትሪዎች ግንባታቸው ቢጠናቀቅም፣ የኤሌክትሪክ ኃይል ባለማግኘታቸው ምክንያት ወደ ሥራ ሊገቡ አለመቻላቸውን አስታወቁ፡፡ ሥራ የጀመሩትም በኃይል አቅርቦት ችግር ኪሳራ ውስጥ እየገቡ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ ይህ የተገለጸው...
View Articleየአዲስ አበባ አስተዳደር በነባሩ ካቢኔ ይቀጥላል
-አቶ ድሪባ ኩማ የከተማውን ቁልፍ ተረከቡ ተመራጩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ከንቲባ አድርጎ ከመረጣቸው ከቀድሞው የትራንስፖርት ሚኒስትር አቶ ድሪባ ኩማ በስተቀር፣ ነባሮቹን የከተማው አስተዳደር ሹማምንት በድጋሚ ሹመታቸውን በማፅደቅ አዳዲስ ፊቶችን ሳያመጣ ቀረ፡፡ ማክሰኞ ሐምሌ 2 ቀን 2005 ዓ.ም....
View Articleበአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስድስት በተፈጠረ ስህተት ቤት ተመዝጋቢዎች በድጋሚ ተጠሩ
-ስህተቱን የፈጠሩ በቁጥጥር ሥር ውለው ተለቀዋል በቅርቡ በተጠናቀቀው በ10/90 እና 20/80 ቤት ፈላጊዎች ምዝገባ ወቅት በአራዳ ክፍለ ከተማ አንድ ወረዳ ውስጥ የምዝገባ መዛባት ተከስቶ ተመዝጋቢዎች በድጋሚ ተጠርተው እንዲስተካከል ተደረገ፡፡ ስህተቱን ፈጥረዋል በሚል የወረዳው ሠራተኞች ታስረው ተለቀዋል፡፡ ችግሩ...
View Articleበኦሮሚያ የሚገኙ የዱቄት ፋብሪካዎች ለኪሳራ የሚዳርገን አሠራር ተፈጠረብን አሉ
‹‹እኛ የምናስፈጽመው የንግድ ሚኒስቴር አዋጅን ነው›› የኦሮሚያ ንግድና ልማት ቢሮ‹‹አሠራሩ ካልተመቻቸው ከትስስሩ መውጣት ይችላሉ›› ንግድ ሚኒስቴርበኦሮሚያ ክልል የሚገኙ የዱቄት ፋብሪካዎች ከአቅም በታች እንዲሠሩ እየተደረጉ መሆኑን በመግለጽ፣ ክልሉ እየዘረጋው ያለው አሠራር ለኪሳራ የሚዳርጋቸው መሆኑን ገለጹ፡፡...
View Articleየአምባሳደር ብርሃኑ ዲንቃ ሥርዓተ ቀብር ቅዳሜ ይፈጸማል
አስከሬናቸው ሐሙስ ይገባል በተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና በአፍሪካ ኅብረት ይሠሩ የነበሩት የአንጋፋው ዲፕሎማት አምባሳደር ብርሃኑ ዲንቃ ሥርዓተ ቀብር የፊታችን ቅዳሜ ሐምሌ 6 ቀን 2005 ዓ.ም. በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈጸማል፡፡ ከትናንት በስቲያ ሰኞ (ሐምሌ 1) በሚኖሩበት ኒው ዮርክ ከተማ...
View Articleለአዲስ አበባ መሥርያ ቤቶች በማዕከል ግዥ የሚፈጽም ኤጀንሲ ሊቋቋም ነው
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሁሉም መሥሪያ ቤቶች የሚካሄዱ ግዢዎችን የሚያስቀር ኤጀንሲ ሊያቋቁም መሆኑን ምንጮች ገለጹ፡፡ ኤጀንሲው የሚቋቋምበት ጥናትና የሕግ ረቂቅ እየተዘጋጀ የሚገኘው በአዲስ አበባ ከተማ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ መሆኑ ታውቋል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 14 ቢሮዎች፣ ባለሥልጣን...
View Articleንግድ ሚኒስቴር የጋምካን የሥራ ፈቃድ አገደ
- በሦስት ቀናት ፈቃዱን ካልመለሰ ከንግድ መዝገብ ይሰረዛል ብሏልንግድ ሚኒስቴር ከፍተኛና መካከለኛ ክሊኒኮችን በመመልመል፣ ለቤት ሠራተኝነት ወደ ዓረብ አገሮች የሚሄዱ ዜጐችን እንዲመረምሩ የሚያሰማራውን የጋምካ ጽሕፈት ሥራ አገልግሎት ድርጅትን ፈቃድ ከሐምሌ 1 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ ማገዱን አስታወቀ፡፡...
View Articleበአቶ መላኩና አቶ ገብረዋህድ የምርመራ መዝገብ ተጨማሪ ተጠርጣሪዎች ተካተቱ
- የአንድ ተጠርጣሪ እህት 1.2 ሚሊዮን ብር ሲያሸሹ መያዛቸው ተገለጸበተጠረጠሩበት ከባድ የሙስና ወንጀል በቁጥጥር ሥር በሚገኙት የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተርና ምክትል ዋና ዳይሬክተር በነበሩት፣ አቶ መላኩ ፈንታና አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስ የምርመራ መዝገብ ተጨማሪ ተጠርጣሪዎች...
View Articleበፕራይቬታይዜሽን የሚሸጡ ድርጅቶች ገቢ ለህዳሴው ግድብ እንዲውል ተወሰነ
-በዚህ ዓመት ከሦስት ቢሊዮን ብር በላይ ከድርጅቶች ሽያጭ ይጠበቃል የመንግሥት የልማት ድርጅቶችን በፕራይቬታይዜሽን ፕሮግራሙ መሠረት በሽያጭ ለግሉ ዘርፍ በማስተላለፍ የሚገኘው ገቢ በአጠቃላይ ለህዳሴው ግድብ እንዲውል መንግሥት ወሰነ፡፡ የፕራይቬታይዜሽን ፕሮግራሙን የሚያስፈጽመው የፕራይቬታይዜሽንና የመንግሥት ልማት...
View Articleዘጠኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ኃላፊዎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ሁለት ከፍተኛ ባለሥልጣናትና ሰባት የምሕንድስና ኃላፊዎች ከትራንስፎርመር ግዥ ጋር በተያያዘ በሙስና ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ዋሉ፡፡ ሐምሌ 2 ቀን 2005 ዓ.ም. በቁጥጥር ሥር ከዋሉት መካከል የኮርፖሬሽኑ የገጠር ኤሌክትሪፊኬሽን ማስፋፊያ ዘርፍ ምክትል ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሽፈራው...
View Articleአራጣ በማበደር ወንጀል 25 ዓመታት የተፈረደባቸው አቶ አየለ ደበላ (አይኤምኤፍ) አረፉ
አራጣ በማበደርና በሌሎችም ክሶች ከአራት ዓመታት በፊት ክስ ተመሥርቶባቸው 25 ዓመታት ተፈርዶባቸው ማረሚያ ቤት የነበሩትና በቅጽል ስማቸው ‹‹አይኤምኤፍ›› በመባል የሚታወቁት አቶ አየለ ደበላ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡ በተወለዱ በ70 ዓመታቸው ሰኔ 30 ቀን 2005 ዓ.ም. ረፋዱ ላይ በእስር ላይ በሚገኙበት በአዲስ...
View Article